User:Hadale'ela Afar Ethiopia
Jump to navigation
Jump to search
Hadale'ela Town ሀደሌኤላ ከተማ
የሀደሌኤላ ከተማ ድሮ ፉርሲ ወረዳ በመባል የሚታወቅ የነበረና አሁን ደግሞ በመቀመጫዋ የተሰየመችዉ የሀደሌኤላ ወረዳ ዋና ከተማ ነች። የሀደሌኤላ ወረዳ ከአዲስ አበባ - መቀሌ ዋናዉ እስፓልት መንገድ 13ኪሚ ርቀት ላይ ወደ ዉስጥ ገባ ብላ የምትገኝ ወረዳ ነች። ወረዳዋ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በዞን 5 መስተዳድር ደቡባዊ ክፍል ትገኛለች። የሀደሌኤላ ወረዳ በምእረብ በአማራ ክልል የኦሮሚያ ልዩ ዞን የጅሌ ጥሙጋ ወረዳን በምስራቅ በአፋር ክልል ቡሪሞዳይቶ ወረዳ ትወስናለች። በደቡብ በኩል በአፋር ክልል ሰሙ ሮቢ ገላእሉ (ኮማሚ) ወረዳን በስተሰሜን በኩል ደግሞ በአፋር ክልል ከዳሌፋጌ ወረዳ ጋር ትወሰናለች።
የሀደሌኤላ ወረዳ በስሩ አስራ አንድ (11) ቀበሌዎችን አቅፋ የሚታስተዳድር ስትሆን የወረዳው አጠቃላይ ህዝብ ብዛት ከ90,000 በላይ ይሆናል ተብሎ ይገመታል።
በቀጣይም ስለወረዳዉ የሚገልፁ ትክክለኛ መረጃዎችን በዚሁ ፔጅ የሚንለቅ ይሆናል።